የኢትዮጵያ ሚዲያ ተደራሽነት ሕጎች እና በምርጫ ወቅት የሚዲያ ተደራሽነት ለምርጫ ባለድርሻ አካላት ላይ የተዘጋጀ የኅብረት ለምርጫ ፖሊሲ ፍሬ ሃሳብ

የኢትዮጵያ ሚዲያ ተደራሽነት ሕጎች እና በምርጫ ወቅት የሚዲያ ተደራሽነት ለምርጫ ባለድርሻ አካላት ላይ የተዘጋጀ የኅብረት ለምርጫ ፖሊሲ ፍሬ ሃሳብ

ይህ የፖሊሲ ማብራሪያ በመገናኛ ብዙሃን እና በምርጫ መካከል ያለውን ግንኙነት አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በኢትዮጵያ 6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያሉትን ተግዳሮቶች፣ አንድምታዎች እና ተስፋዎች እና የመገናኛ ብዙሃን የተለያዩ የምርጫ ባለድርሻ አካላትን ተደራሽነት ይዳስሳል። ከዚህ ባለፈም የሚዲያ ተቋማት የጋዜጠኝነት ሞያ ስነ-ምግባር አክብረው በምርጫው ሂደት ላይ ሚዛናዊ ሽፋን መስጠት እንዳለባቸው ያትታል። በተጨማሪም የመራጮች ትምህርት የሚዲያ ሽፋን ማሳደግ እና ሴቶችን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በምርጫ ወቅት በሚዲያ ሽፋን በበቂ ሁኔታ እንዲወከሉ የማድረግን አስፈላጊነት አጉልቶ ያሳያል።

በኅብረት ለምርጫ የሚዲያ ክትትል ክፍል ዘገባ ላይ በመመስረት፤ 6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ በተካሄደበት ወቅት፣ ከምርጫ ጋር የተያያዙ ርዕሰ ጉዳዮች ብዙውን ጊዜ በመገናኛ ብዙኃን ሽፋን ቢያገኙም፤ ነገር ግን የሚዲያ ሽፋን በሌሎች ከምርጫ ጋር ያልተገናኙ የፖለቲካ ጉዳዮች () አብላጫ የሆኖ ሽፋን አግኝተው ነበረ። በምርጫ ክርክሮች ላይ 12 የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢሳተፉም በትላልቅ የክርክር መድረኮች 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች ብቻ ነበር የተሳተፉት። የጋዜጠኝነት ሞያዊ ሥነ ምግባርን አክብሮ መዘገብ ላይ ከሚዲያ ሚዲያ ልዩነት ነበረ። ከዚህም ባለፈ አብዛኛው ሚዲያ የምርጫ ቅስቀሳን ሚዛናዊነት በጠበቀ መልኩ ከመገናኛ ብዙሀን ህጎች እና ከምርጫ ቦርድ መመሪያዎች ጋር በተስማማ ሁኔታ ማቅረብ አልቻሉም ነበር። ገዥው ብልፅግና ፓርቲ ከሌሎች የምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛውን ሽፋን ያገኘ ሲሆን በተጨማሪም ሚዲያዎች ከምርጫ ጋር በተገናኘ ለሴቶች የሰጡት ሽፋን በጣም አነስተኛ ነበር፡፡

በኢትዮጵያ የሚዲያ ዘርፍ በምርጫ ወቅት ተገቢውን ሚና እንዲጫወት ለማድረግ ከቀደምት የስኬት ተሞክሮዎች ትምህርት በመውሰድ እና በመጪው ምርጫ የሚዲያው ዘርፍ የላቀ ሚና እንዲኖረው መሻሻል በሚገባቸው ዘርፎች ላይ አተኩሮ ሊሰራ ይገባል። ይህ ካልሆነ ግን ሚናው ተቆርጦ በቀደመው ምርጫ ወቅት እንደነበረው ይቆያል።

CECOE Policy Brief on: Ethiopian Media Accessibility Laws and the Electoral Stakeholders’ Access to Media During Elections

CECOE Policy Brief on: Ethiopian Media Accessibility Laws and the Electoral Stakeholders’ Access to Media During Elections

Considering the importance of the relationship between the Media and Elections, this policy brief examines the challenges, implications, and prospects in the context of the 6th elections of Ethiopia and media access to various electoral stakeholders. Furthermore, it highlights the need for media outlets to adhere to ethical and journalistic standards and provide balanced coverage of the electoral process. It also underscores the importance of increasing media coverage of voter education and ensuring that all stakeholders, including women are adequately represented in media coverage during election periods.

Based on CECOE’s Media Monitoring Unit report, during the period where the 6th general elections were held, election-related topics were often discussed in the media. However, the media coverage was dominated by other political issues(non-election related). While twelve political parties participated in the election debates, only 5 parties frequently participated in major debates. The degree of obeying journalistic ethics and code of conduct varied from one media outlet to another. Furthermore, most media outlets failed to cover the election campaign in a balanced manner contrary to the stipulations of the media laws and NEBE’s directives. The ruling party, Prosperity Party, received the largest amount of coverage compared to other stakeholders. Additionally, media coverage about women was very scant.

In order to play its rightful role, the Ethiopian media sector must draw lessons from its success stories and work on areas that require improvement to have an increased role in the upcoming elections. Otherwise, its role will be curtailed and remain where it was during the previous election.