የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የእኩለ ቀን የትዝብት ሪፖርት

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ (ኅብረት ለምርጫ)፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአገር በቀል የዜጎች ምርጫ ትዝብት (Citizen Election Observation) ለማከናወን፤ 2,258 ተቀማጭ (Sitting Observers) እና 891 ተንቀሳቃሽ (Mobile Observers) ታዛቢዎችን፣ በአጠቃላይ 3,149 ታዛቢዎችን አሰማርቷል።

የኅብረቱ ተቀማጭ ታዛቢዎች በተመደቡባቸው የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከንጋቱ 11፡30 ጀምሮ የጣቢያዎቹን አደረጃጀትና አከፋፈት፣ የድምፅ አሰጣጥና የቆጠራ ሂደቱን፣ እንዲሁም በጣቢያ ደረጃ የሚከናወነውን ይፋዊ የውጤት መለጠፍ ተግባር ይታዘባሉ። በሌላ በኩል፣ እያንዳንዱ ተንቀሳቃሽ ታዛቢ ቢያንስ ስድስት (6) የተለያዩ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎችን በመዘዋወር እንዲታዘብ ተመድቧል።

የኅብረቱ ታዛቢዎች ስምሪት፤ ከትግራይ ክልል፣ በአማራ ክልል ከሚገኙ ስምንት (8) የምርጫ ክልሎች፣ እንዲሁም አከራካሪ ከሆኑ 5 የምርጫ ክልሎች ውጭ ባሉ የምርጫ ክልሎችን የተከናወነ ነው። ይህ የስምሪት ስልት በየክልሎቹ ያለውን የምርጫ ጣቢያዎች ብዛት መሠረት ባደረገ ተመጣጣኝ (proportional) ትዝብት ዘዴ ላይ የተመሠረተ ነው። 

ይህ የእኩለ ቀን የትዝብት ሪፖርት መሰረት ያደረገው የኅብረቱ ታዛቢዎች በተሰማሩባቸው 2,258 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ላይ ብቻ ነው። ኅብረቱ ካሰማራቸው ተንቀሳቃሽ ታዛቢዎች የሰበሰባቸው መረጃዎች አሳሳቢ ሁነቶች ላይ የተደረጉ ሪፖርቶች ብቻ ነው። የኅብረት ለምርጫ የመረጃ ማዕከል በድምጽ መስጫ ቀን እስከ ቀኑ 7 ሰዓት ድረስ ከተቀበላቸው 2,258 ተቀማጭ ታዛቢዎች (Stationary Observers) ባቀረቧቸው ሪፖርቶች ላይ ተመስርቶ ተዘጋጅቷል። 

በሚጠበቁ ነገር ግን በዘገዩ መረጃዎች ምክንያት ይህ ሪፖርት ያላካተታቸው የትዝብት ግኝቶች ያሉ ሲሆን ዘግይተው የሚደርሱ መረጃዎች ኅብረቱ በሚያወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ውስጥ ተካተው የሚቀርቡ ይሆናል። ይህ የእኩለ ቀን ሪፖርት የኅብረቱ ታዛቢዎች በተሰማሩባቸው 2,258 ጣቢያዎች አስር (10) ዋና አመላካቾች (Indicators) ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ነው። 

ዋና ዋና የእኩለ ቀን ትዝብት ግኝቶች

  1. ታዛቢዎች ወደ ድምጽ መስጫ ጣቢያ በመግባት እንዲታዘቡ መፈቀድ

የምርጫ ህጉ ከቦርዱ እውቅና የተሰጣቸው የምርጫ ታዛቢዎች በተመደቡበት የድምፅ መስጫ ጣቢያ ገብተው ሂደቱን በነፃነት መታዘብ እንደሚችሉ ይደነግጋል። የኅብረቱ ታዛቢዎች ወደ ምርጫ ጣቢያ ገብተው እንዲታዘቡ መፈቀድን በተመለከተ፣ ከተቀብልናቸው ሪፖርቶች መካከል 2,241 (99%) የሚሆኑት ያለምንም ገደብ ወደ ጣቢያዎቹ ገብተው መታዘብ ችለዋል።

በተቃራኒው ግን 17 (1%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች እንዳይገቡ መከልከላቸውን ታውቋል።

  1. በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች መክፈቻ ሰዓት የምርጫ አስፈጻሚዎች ተሟልቶ መገኘት

የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች በሕግ በተደነገገው የመክፈቻ ሰዓት ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ከመከፈታቸው በፊት የምርጫ አስፈፃሚዎች በቦታው መገኘት ይጠበቅባቸዋል። ይህ የምርጫ ጣቢያው በወቅቱ እንዲዘጋጅ፣ የምርጫ ቁሳቁሶች እንዲደርሱ እና የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በሥርዓት እንዲጀመር ቅድመ ሁኔታ ነው። ኅብረቱ ከተቀበላቸው የትዝብት ረፖርቶች ውስጥ 2,183 (97%) የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች፣ የኅብረቱ ታዛቢዎች በምርጫ ጣቢያ ሲደርሱ የምርጫ አስፈጻሚዎች በቦታው እንደነበሩ ታዝበናል።

በተቃራኒው፣ 50 (2%) የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች፣ የኅብረቱ ታዛቢዎች ሲደርሱ የምርጫ አስፈጻሚዎች ከመክፈቻው ሰዓት (ንጋት 12 ሰዓት) በቦታው እንዳልተገኙ ታዝበናል። 

  1. ድምጽ መስጠት በሚጀመርበት ሰዓት (ከጠዋቱ 12 ሰዓት) በጣቢያዎች የተገኙ አስፈጻሚዎች ቁጥር

የድምፅ አሰጣጥ በሚጀምርበት ወቅት በ2,146 (95%) የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከ3 በላይ የምርጫ አስፈጻሚዎች በህጉ በተደነገገው መሰረት በቦታው ተገኝተው ሥራ መጀመራቸውን ኅብረቱ ታዝቧል። በአንጻሩ 90 (4%) ጣቢያዎች ውስጥ ደግሞ 3 የምርጫ አስፈጻሚዎች በምርጫ ጣቢያዎች መገኘታቸው ሲረጋገጥ፣ በተቃራኒው በ22 (1%) የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ውስጥ ከ3 በታች የምርጫ አስፈጻሚዎች መገኘታቸውን መታዘብ ተችሏል።

  1. የምርጫ አስፈፃሚዎች የፆታ እና የአካል ጉዳተኝነት ስብጥር

ከታዘብናቸው የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል በ1,380 (61%) ጣቢያዎች ከ1 በላይ ሴት የምርጫ አስፈጻሚዎች ሲገኙ፤ በአንጻሩ 697 (31%) ድምጽ መስጫ ጣቢያ 1 ሴት አስፈጻሚ እንደነበረች ታዝበናል። በተቃራኒው በ181 (8%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ውስጥ ደግሞ ምንም ዓይነት ሴት የምርጫ አስፈጻሚዎች እንዳልተመደቡ ታዝበናል።

ትዝብት ከተደረገባቸው የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል 76 (3%) በሚሆኑት ከ1 በላይ አካል ጉዳተኛ የምርጫ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል። በሌላ በኩል 224 (10%) ጣቢያዎች ውስጥ 1 አካል ጉዳተኛ አስፈጻሚ መገኘታቸውን ታዝበናል። በአንጻሩ በ1,958 (87%) ጣቢያዎች ደግሞ ምንም ዓይነት አካል ጉዳተኛ የምርጫ አስፈጻሚ እንዳልነበረ መታዘብ ተችሏል።

የምርጫ ጣቢያ ኃላፊዎች የጾታ ስብጥርን በሚመለከት፣ በ587 (26%) ጣቢያዎች ውስጥ የድምጽ መስጫ ጣቢያው ኃላፊ ሴት ነበረች። በተመሳሳይ ሁኔታ በ54 (2%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች አካል ጉዳተኛ ሴቶች በጣቢያ ኃላፊነት መስራታቸውን፣ በ65 (3%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ አካል ጉዳተኛ ወንዶች የጣቢያ ኃላፊ ሆነው መስራታቸውን ታዝበናል።

  1. የድምፅ መስጠት አጀማመር

ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል፣ በ947 (42%) ጣቢያዎች የድምፅ መስጠት ሂደቱ ከጥዋቱ 12 ሰዓት በፊት መጀመሩን፣ በ1,276 (57%) ጣቢያዎች ደግሞ ከጥዋቱ 12 እስከ 1 ሰዓት ባለው ግዜ መጀመሩን ኅብረቱ ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 32 (1%) ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት በኋላ መጀመሩን ኅብረቱ የታዘበ ሲሆን በ3 ጣቢያዎች ይህ መግለጫ እስከተዘጋጀበት ሰዓት ድረስ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እንዳልተጀመረ ለመታዘብ ተችሏል።

  1. የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የተቋቋሙበት ሥፍራ

በምርጫ ህጉ መሰረት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች በወታደራዊ ካምፕ፣ ፖሊስ ጣቢያ፣ የሃይማኖት ተቋም፣ የጤና ተቋም፣ መጠጥ ቤት/ሆቴል፣ የፖለቲካ ፓርቲ ጽ/ቤት ወይም የግለሰብ መኖሪያ ቤት ማቋቋም የተከለከለ ነው። 

ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 ጣቢያዎች መካከል፣ 2,182 (97%) ጣቢያዎች በሕግ በተፈቀዱ ቦታዎች መቋቋማቸውን ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 76 (3%) ጣቢያዎች በሕግ በተከለከሉ ቦታዎች መቋቋማቸውን ታዝቧል።

  1. በድምጽ መስጫ ጣቢያ ውስጥ ወይም በ200 ሜትር ርቀት ክልል ውስጥ የቅስቀሳ ምልክቶች እና ቅስቀሳዎች መኖራቸውን በተመለከተ

ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 ጣቢያዎች መካከል፣ 2,171 (96%) ጣቢያዎች በምርጫ ጣቢያው ውስጥ ወይም በ200 ሜትር ርቀት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ ቅስቀሳ ምልክቶች (ፖስተር) ወይም ቅስቀሳዎች አለመከናወናቸውን ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 87 (4%) ጣቢያዎች ውስጥ ወይም በ200 ሜትር ርቀት ክልል ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ ቅስቀሳ ምልክቶች፣ ቁሳቁሶች ወይም የቅስቀሳ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ታዝበናል።

  1. የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ተደራሽነት እና አመቺነት በተመለከተ

በምርጫ ህጉ መሰረት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች በሕግ በተፈቀዱ ቦታዎች መቋቋም፣ ለመራጮች በቀላሉ ተደራሽ መሆን እና መሠረታዊ የምርጫ ቁሳቁሶች ተሟልተው መገኘታቸው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሥርዓት እንዲካሄድ አስፈላጊ ነው። በተለይ ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለአረጋውያን፣ ለነፍሰ ጡሮች እና ጨቅላ ሕፃን ለያዙ ወላጆች ተደራሽነት መኖሩ የሁሉንም ዜጎች ተሳትፎ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው።

የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የተቋቋሙበት ስፍራ ለሴቶች ያላቸውን አመቺነትን በተመለከተ ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 ጣቢያዎች መካከል፣ 2,157 (96%) ጣቢያዎች ለሴቶች ምቹ እንደነበሩ ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 101 (4%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ለሴቶች አመቺ እንዳልነበሩ መታዘብ ተችሏል።

የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ለአካል ጉዳተኞች ያላቸውን ተደራሽነት በተመለከተ፣ ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል፣ 2,110 (93%) ጣቢያዎች አካል ጉዳተኞች ያለ ረዳት በመግባት ድምፅ ለመስጠት ምቹ እንደነበሩ ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 148 (7%) ጣቢያዎች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እንዳልነበሩ ታዝበናል።

ጣቢያዎች ለአረጋውያን፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ጨቅላ ሕፃን ለያዙ ወላጆች እና የመንቀሳቀስ ችግር ላለባቸው መራጮች ያላቸውን አመቺነት በተመለከተ 2,158 (96%) ጣቢያዎች ምቹ እንደነበሩ ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 100 (4%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች በዚህ ረገድ ችግር እንደነበረባቸው ለመታዘብ ተችሏል።

  1. ሁሉም የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶች መሟላታቸውን በተመለከተ

ኅብረቱ ትዝብት መሠረት፣ የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ የቦርዱ ማህተም፣ የማይለቅ የጣት ቀለም፣ የድምፅ መስጫ ማሸጊያዎች፣ የመራጮች መዝገብ እና የቦርዱ ድምፅ መስጫ ሳጥኖች ጨምሮ የምርጫ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ በታዘቡት ጣቢያዎች መገኘታቸው ተረጋግጧል። በተቃራኒው፣ የውጤት መግለጫ እና ማመሳከሪያ ፎርም 99% (1,693) ሲገኝ በ1% (11) ጣቢያዎች ላይ አልተገኘም፤ እንዲሁም የቅሬታ ማቅረቢያ እና ምስክርነት መቀበያ ፎርም 99% (1,680) ሲገኝ በ1% (24) ጣቢያዎች ላይ አለመገኘቱ ተመዝግቧል። 

  1. የድምፅ መስጫ ሳጥኖች ከመታሸጋቸው በፊት ባዶ መሆናቸውን ማረጋገጥን በተመለከተ

ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,258 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል፣ 2,232 (99%) ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ሳጥኑ ከመታሸጉ በፊት ባዶ መሆኑ ታዝቧል። በተቃራኒው፣ 26 (1%) የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ሳጥኑ ከመታሸጉ በፊት ባዶ መሆኑ በግልፅ እንዳልታየ መታዘብ ተችሏል። በ2,253 ጣቢያዎች የድምጽ መስጫ ማሸጊያዎች መገኘታቸው የታዘብን ሲሆን በ5 ጣቢያዎች ደግሞ የድምጽ መስጫ ማሸጊያዎች አለመገኘታቸውን ታዝበናል።

አሳሳቢ ሁነቶች

ይህ የእኩለ ቀን ሪፖርት በሚዘጋጅበት ጊዜ፣ ኅብረት ለምርጫ ከመክፈቻና ከዝግጅት ሂደት ጋር የተያያዙ  በጠቅላላው 203 አሳሳቢ ሁነቶችን የተቀበለ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 40 ያህሉ የተረጋገጡ ናቸው። ሪፖርቶ የተደረጉ 163 ጉዳዮች ገና በማረጋገጥ ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን ኅብረቱ በሚያወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ የሚያደርግ ይሆናል። 

  1. በተከለከለ ቦታ የተቋቋሙ ጣቢያዎች

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጾኪያና ገምዛ  ምርጫ ጣቢያ የተቋቋመው ጤና ጣቢያ ውስጥ ሲሆን ስሙም መኮይ ጤና 3 ለ _1 ምርጫ ጣቢያ ይባላል። በአዲስ አበባ የካ ወረዳ 1 የሚገኝ ምርጫ ጣቢያ የተቋቋመው በጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ በተተከል ድንኳን ነው። በድሬደዋ ከተማ አስተደደር ወረዳ 02 የሚገኝ የምርጫ ጣቢያ ሳቢያን አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ አንድ ክፍል በመውሰድ ምርጫ እየተደረገ ይገኛል።

  1. በጣቢያዎች ውስጥ ወይም 200 ሜትር ርቀት ላይ ቅስቀሳ ማድረግ

በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ  ወረዳ 4 ምርጫ ጣቢያ ሠፈረ ሰላም ቅድመ አንደኛ ት/ቤት የብልፅግና ፓርቲ ወኪል የቅስቀሳ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ ታዝበናል። በተመሳሳይ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሚገኝ ምርጫ ጣቢያ 0851207010120 የብልፅግና ፓርቲ ታዛቢ መራጮች ለመምረጥ በተሰለፉበት የምርጫ ቅስቀሳ ሲይያደርግ ታይቷል።

  1. ታዛቢዎች ወደጣቢያ እንዳየግቡ መከልከል  

የኅብረቱ ታዛቢ ወልዲያ ጉዲና ምርጫ ጣቢያ እንዳይገባ የተከለከለ ሲሆን ቀደም ብሎ ምርጫ ጣቢያ ሲደርስ ለምርጫ አስፈጻሚው የመጣበትን ቢናገርም እንዲሁም መታወቂያ ቢያሳይም እንዲገባ አልተፈቀደለትም። 

በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባ ቦራ ዞን አልጌ ሳቺ ወረዳ በጣቢያ መ.ቁ 422111281401 ታዛቢያችን በሰዓቱ በጣቢያው ቢደርሱም በምርጫ አስፈጻሚው ወደ ምርጫ ጣቢያ እንዳይገቡ ተከልክሏል።

በኦሮሚያ ክልል በኢሉ አባ ቦራ ዞን ኤልጌ ሰቸ ወረዳ በ አልጌ ምርጫ ጣቢያ በምርጫ ጣቢያ ቁጥር 422111281401 ታዛቢው ጠዋት 12፡00 ሰዓት ደርሰው እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው ከገቡ በኋላ እዚያው ቁጭ ብለው እንዲታዘቡ ባለመፍቀድ ታዛቢውን አስወጥተዋቸዋል። 

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አዳሜ ምርጫ ጣቢያ ሀ 1 ታዛቢው የቀበሌ መታወቂያ አልያዝኩም ነገር ግን ሙሉ ስም የሚገልጽ ፎቶ ያለው የመስሪያ ቤት መታወቂያ ከኅብረቱ የትዝብት ባጅ ጋር ቢያሳይም የቀበሌ መታወቂያ ካላመጡ እንደማይታዘቡ ተነግሯቸው ወደ ምርጫ ጣቢያ ገብቶ ለመታዘብ ተከልክለዋል።  

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን ዱና ወረዳ ጨፍሜራ ክራይ ቤት ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 0748215020104 ታዛቢዋ ባጅ ላይ የሚታዘቡብት ቦታ በባጁ ላይ አልተጠቀሰም በሚል ምክንያት ገብተው መታዘብ ተከልክለዋል፡፡ 

  1. ከምርጫ ጣቢያ ኃላፊ ውጭ የተደረገ ተደጋጋሚ ዕገዛ 

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ምርጫ ጣቢያ ሠፈረ ሰላም ቅድመ አንደኛ ት/ቤት ያልተፈቀደላቸው ግለሰቦች ለመራጮች ተደጋጋሚ ዕገዛ ሲይደርጉ ነበር። 

በአዲስ አበባ በቂርቆስ ከፍለ ከተማ ወረዳ 03 በ እድር ቤት ምርጫ ጣቢያ  አንድ ዕገዛ እንድታደርግ ያልተፈቀደላት ሴት ከ14 በላይ መራጮች ስትረዳ ከቆየች በኋላ የጣቢያው ኃላፊ እንድትወጣ ተደርጋለች። 

በሰሜናዊ ሲዳማ ጎርቼ ወረዳ ዶና ምርጫ ጣቢያ  ልዩ ስሙ ጎርቼ 01  ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 0850910042012 ሰልፍ አስከባሪው ለ30 መራጮች እርዳታ ሲሰጡ አረጋግጠናል። በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ቡርቃ ጃቶ በምርጫ ጣቢያ ቁጥር 0432405390101 የምርጫ አስፈፅሚ እርዳታ ለሚፈልጉትም ለማይፈልጉትም እየገባ ከአንድ ጊዜ በላይ እገዛ ሲሰጥ ታይቷል። በአማራ ክልል አዊ ዞን ዝገም ወረዳ በምርጫ ጣቢያ ቁጥር 0315105111302 ለመራጮቹ ካርድ የሚሰጡት ምርጫ አስፈፃሚዎች ለ10 መራጮች ምልክት እያደረጉ ሲሰጡ መታዘብ ተችሏል።

  1. የድምጽ መስጫ ሳጥኖች ባዶ መሆናቸውን ሳይረጋገጡ ማሸግ 

ኦሮሞያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ሃሩ ወረዳ ገነት አቦ ቀበሌ ገነት አቦ ምርጫ ጣቢያ ኮድ 0426401691801 ታዛቢያችን ባደረጉት ትዝብት የድምፅ መስጫ ሳጥን ባዶ መሆኑን ሳያሳዩ ማስጀመራቸውን ለመታዘብ ችለዋል። 

  1. የድምጽ መስጫ ወረቀቶችን ማህተም ሳያደርጉ ማደል 

አዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7ተስፋ ብርሃን ሸማቾች ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 1452706030103 ታዛቢያችን ጠዋት 1፡30 ላይ ባደረጉት ትዝብት 15 የሚሆኑ መራጮች የተሰጣቸው የድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ምንም አይነት ማህተም እንደሌው ለመታዘብ ችለዋል።  

  1. የድምጽ መስጫ ጣቢያ ቁሳቁሶች መቀያየር 

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ አያት ዞን 3  ንኡስ ምርጫ ጣቢያ  ምርጫ ክልል 28  የተወዳደሩት እጩዎች ወደ ምርጫ ክልል 17  ተሳስቶ በመላኩ እስኪስተካከል ድረስ ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ድምጽ መቀጠሉን ታዝበናል።

  1. የጸጥታ መደፈርስ 

ከጸጥታ መደፍረስ ጋር በተገናኘ በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ወገራ ወረዳ አምባጊዮርጊስ ከተማ ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 031750508100 (ቀበሌ 02) ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ድምፅ መስጠት ቢጀመርም፣ ከረፋዱ 5፡10 ጀምሮ በጣቢያው አቅራቢያ በተሰማ ተኩስ ምክንያት ሂደቱ ተቋርጧል። 

በተመሳሳይ በሰሜን ወሎ ጋዞ ወረዳ መቄት 2 ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 0314019071101 ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በነበረ ተኩስ ለ40 ደቂቃ ያህል ሂደቱ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ በዚሁ ወረዳ በሌላ ጣቢያ ደግሞ ከጠዋቱ 12፡30 እስከ 1፡10 ድረስ በተሰማ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ምክንያት የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ተቋርጦ ከጠዋቱ 1፡30 በኋላ ሂደቱ ቀጥሏል። 

በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣ ወረዳ (ጣቢያ ቁጥር 0310718140216) በተኩስ ድምጽ ምክንያት ሂደቱ ሲቋረጥ፣ በፎገራ ወረታ ከተማ (ጣቢያ 0311116140402)። 

በደብረ ታቦር ከተማ ቀበሌ 4 ጣቢያዎችም በተመሳሳይ ምክንያት አስፈጻሚዎች ጣቢያዎቹን ዘግተው ለመውጣት ተገደዋል። በደብረ ታቦር ያለው ጣቢያ በ3፡00 ሰዓት ድጋሚ ስራ የጀመረ ሲሆን፣ በእናቲቱ ማርያም ጣቢያ (0310718140107) ደግሞ በ2፡35 በተከፈተ ተኩስ ሰራተኞች ንብረት ጭነው በመውጣታቸው ሂደቱ ተቋርጧል። 

  1. ያልተፈቀደላቸው ግለሰቦች በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች 

በ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ በአቀስታ ምርጫ ጣቢያ አንድ በ ምርጫ ኮድ 013403070301ላይ ያልተፈቀደላቸው የመንግስት አመራሮች ገብተው አይተው ወጥተዋል።

በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ቱላ ወረዳ መሳፍንት ዘለቀ ኪራይ ቤት ምርጫ ጣቢያ በምርጫ ኮድ 851206011111 ላይ ያልተፈቀደላቸው የቀበሌው አመራሮች ወደ ሚስጥራዊ ድምጽ መስጫ ቦታ በመሄድ መራጮችን ሲያስገድዱ እንደነበር ታዝበዋል።

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ለተጨማሪ መረጃ፦
የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ /ኅብረት ለምርጫ /
ኢሜይል: info@cecoe.org | www.cecoe.org

CECOE has launched the Digital Election Observation Workspace (DEOW)

CECOE has launched the Digital Election Observation Workspace (DEOW)

CECOE has launched the Digital Election Observation Workspace (DEOW) to support and improve its election observation process. As CECOE continues deploying observers across the country, DEOW provides a more structured and efficient system for managing key processes — from recruitment to communication and reporting. The platform includes easier recruitment and management of observers, automated generation of checklists and certificates and samelined communication through broadcast and notification messages. From 27–29 April 2026, the CECOE team received training on the system management.

This was followed by an official handover ceremony between Executive Director Ato Abera Hailemariyam and Dr. Marco Hoase, Head of the Programme, Support to Good Governance (S2GG) Programme. In his remarks, Ato Abera highlighted the importance of this partnership, noting that DEOW will significantly strengthen and digitalize CECOE’s observation efforts — making them more advanced, organized, and impactful.

The platform is expected to improve coordination and timeliness in election observation activities of CECOE, while supporting the deployment of a larger number of observers. The development of DEOW was supported by the GIZ-implemented Support to Good Governance (S2GG) Programme.

Observation Finding Report on Voter Registration Processes for the Seventh General Elections of Ethiopia

Introduction

The Coalition of Ethiopian Civil Society Organizations for Election (Coalition for Election), under the accreditation obtained from the National Election Board of Ethiopia (NEBE), is observing the Seventh General Elections. The Coalition has deployed 522 long-term observers (LTOs)  to  observe  the voter registration process across all Ethiopian regions and the two city administrations, Addis Ababa and Dire Dawa  with the exception of the Tigray region and contested areas.

This report evaluates the voter registration process conducted by the NEBE —assisted by both manual and tablet methods—in a systematic manner using consistent observation checklists based on key indicators. This report primarily examines the voter registration process, its inclusiveness (participation of women, persons with disabilities, and the elderly), the deployment of security forces around registration centers, and election security.

The report covers the voter registration process from March 20, 2026, to the conclusion of registration on April 22, 2026. It is based on findings gathered from 3,953 manual and 443 tablet registration centers, totaling 4,396 centers where the Coalition  deployed its 522 long-term observers. Any percentage (%) findings presented in this report are calculated relative to the 3,953 manual and 443 tablet registration centers observed by the Coalition.

Organization and Accessibility of Registration Centers

Location of Centers: Regarding the establishment of registration centers, 3,851 (97%) of observed manual centers and 429 (97%) of tablet centers were established in legally permitted locations. However, 102 (3%) manual and 14 (3%) tablet centers were established in prohibited locations (military, police, religious sites, health centers, bars/hotels, political party offices, and private residences).

Availability of Election Officials: The law stipulates that at least three (3) election officials must be present at registration centers. The Coalition’s observers confirmed an average of 4 officials were present at centers under both registration methods.

Opening Hours: 1,284 (63%) manual centers and 125 (56%) tablet centers began registration between 8:30 AM and 9:30 AM. Conversely, 762 (37%) manual centers and 98 (44%) tablet centers started between 9:30 AM and noon (6:00 local time). In 5 observed manual centers, the registration process had not begun by noon.

Lunch Breaks: Of the 1,902 manual and 220 tablet centers observed during the afternoon session, 1,702 (89%) manual centers utilized the legal one-hour lunch break, while the Coalition observed that 200 (11%) centers took more than one hour. Regarding tablet centers, 205 (93%) used the legal one-hour break, while 15 (7%) were found to have exceeded it.

Closing Hours: Among the centers observed in the afternoon, 1,686 (89%) manual and 193 (88%) tablet centers closed between 5:30 PM and 6:00 PM. Our findings show 137 (7%) manual and 17 (8%) tablet centers closed after 6:00 PM. Conversely, 79 (4%) manual and 10 (5%) tablet centers closed before 5:30 PM.

Interruption of Process: In 2,666 (67%) manual centers and 320 (72%) tablet centers, the registration process was never interrupted. Conversely, registration was interrupted at least once in 1,287 (33%) manual and 123 (28%) tablet centers.

Shelter from Sun and Rain: 2,324 (59%) manual and 268 (60%) tablet centers provided shelter (shade) to protect registrants from sun/rain. In contrast, 1,629 (41%) manual and 175 (40%) tablet centers had no such shelter. Convenience for Women: Regarding proximity to residence and safety concerns, 3,563 (90%) manual and 400 (90%) tablet centers were convenient for women; 390 (10%) manual and 43 (10%) tablet centers were not.

Accessibility for those with Limited Mobility: Only 437 (11%) manual and 88 (20%) tablet centers were accessible to registrants with limited mobility (the elderly, pregnant women, or parents with infants). Conversely, 3,516 (89%) manual and 355 (80%) tablet centers were not accessible to these community members.

Accessibility for Persons with Disabilities: The Coalition observed that 485 (12%) manual and 103 (23%) tablet centers allowed persons with disabilities to enter without assistance, whereas 3,468 (88%) manual and 340 (77%) tablet centers were inaccessible without assistance.

Observer Access: Coalition observers were allowed entry without restriction in 3,927 (99%) manual and 430 (97%) tablet centers. However, access was denied in 26 (1%) manual and 13 (3%) tablet centers.

Security Personnel: Security forces were observed outside 2,999 (76%) manual and 320 (80%) tablet centers. Regular police members were present outside 2,003 (51%) manual and 219 (49%) tablet centers. In the remaining 24% of manual and 32% of tablet centers, security forces other than regular police were present. In 25% of manual and 19% of tablet centers, neither police nor other security forces were present outside.

Incidents of Violence/Harassment: In 99.7% of manual and 99% of tablet centers, no violence, threats, or harassment occurred. However, incidents were reported in a small number of centers involving election officials: one (1) murder (East Gojjam, Amhara); two (2) attempted murders (Awi and Wag Hemra, Amhara); seven (7) abductions/kidnappings (2 in East Gojjam, 2 in Wag Hemra, 2 in West Wollega, Oromia, and 1 in South Omo, South Ethiopia); one (1) beating (North Sidama, Sidama); and six (6) threats (South Wollo, North Wollo, West Gojjam, South Gondar, and South Omo).

Voter Registration Process

Identification Documents: Legally, registrants must provide a Kebele ID, passport (even if expired), driver's license, military discharge papers, or student ID. In 3,451 (87%) manual centers, registration followed these rules. However, in 494 (12.49%) manual centers, between 1 and 20 people registered without providing these documents, and in 8 centers, more than 20 people registered without verifying identity/residency.

Digital Registration (OTP): For tablet registration, Fayda National ID holders should receive a One-Time Password (OTP) on their phones. In 424 (96%) tablet centers, OTPs were sent without disruption during observation. However, in 13 (3%) centers, 1–20 registrants did not receive an OTP, and in 6 (1%) centers, more than 20 registrants did not receive it.

Digital Registration (Fayda-less): In 412 (93%) tablet centers, officials successfully entered data (name, age, photo, etc.) for those without Fayda IDs. In 26 (6%) centers, officials were unable to enter data for 1–20 registrants, and in 5 (1%) centers, the system rejected evidence for more than 20 registrants.

Registration Cards: The law dictates cards must be issued immediately upon completion. This occurred in 97% of manual centers, but 111 (3%) centers failed to issue them immediately to 1–20 registrants, and 11 (0.2%) centers failed for more than 20 registrants.

Unauthorized Persons: Only registrants, Board officials, party agents, and accredited observers are allowed inside. This was respected in 98% of manual and 96% of tablet centers. However, unauthorized persons (Kebele leaders, security forces, local party coordinators) were found in 83 (2%) manual and 19 (4%) tablet centers.

Physical Presence: Registration must be done in person. While this was followed in most centers, 92 (2%) manual and 12 (3%) tablet centers registered individuals who were not physically present.

Inclusiveness

Gender Parity among Officials: On average, there was one female official out of the four per center. Women served as heads of 672 (17%) manual centers and 109 (25%) tablet centers.

Persons with Disabilities (Officials): Persons with disabilities served as officials in 93 (0.02%) manual and 15 (0.03%) tablet centers, including roles as center heads.

Female controllers/searchers were present in 97% of manual and 98% of tablet centers. They were missing in 4% of manual and 2% of tablet centers.

Assisted Registration Disclosure: The law requires that information for those registering with assistance be read aloud. This was practiced in 46% of manual and 37% of tablet centers but was ignored in 54% of manual and 63% of tablet centers.

Participation of Stakeholders

Political Parties: Party agents were present in only 539 (14%) manual and 61 (14%) tablet centers. They were absent in 86% of centers for both methods.

Civil Society: Excluding the Coalition’s observers, other observers were present in 156 (8%) manual and 52 (12%) tablet centers. They were absent in 92% of manual and 88% of tablet centers.

Strengths, Areas for Improvement, and Recommendations

Strengths

  • Preparation of a legal framework for digital registration, introduction of technology, and its implementation.
  • Over 5.5 million citizens registered through the digital option.
  • Over 50.5 million total voters registered, 46% of whom are women.
  • Most registration centers were established in legally permitted locations.
  • Observation that most centers were staffed by an average of 4 officials.
  • 87% of observed centers required proper identification for registration.
  • Observer access was granted without restriction in over 97% of centers.

Areas for Improvement

  • Frequent interruptions in the digital registration system.
  • Establishment of a small number of centers in prohibited locations.
  • Instances of registration without identity verification or physical presence, and the presence of unauthorized persons.
  • Inaccessibility of many centers for persons with disabilities and those with limited mobility.
  • Incidents of murder, threats, and abductions against officials and voters by armed forces.

Recommendations

To the National Election Board of Ethiopia (NEBE):

  • Strengthen digital registration infrastructure immediately to resolve system interruptions.
  • Enforce identity verification and physical presence requirements; take legal action against those who violate these laws.
  • Strictly monitor and ensure registration centers are established only in permitted locations.
  • Ensure polling stations for Election Day are accessible to persons with disabilities and strictly follow the protocol of reading registration information aloud for those receiving assistance.
  • Improve election officials’ attendance and punctuality through continuous monitoring and training.
  • Ensure all centers provide shelter from sun and rain.

To Regional Governments:

  • Ensure polling stations are in legal locations, are accessible to persons with disabilities, and provide shelter as required by law.

To Security Forces:

  • Provide adequate protection to prevent threats and attacks against officials, voters, and observers.
  • Deploy regular police members outside polling stations for security.

To Political Parties and Civil Society:

Fulfill the responsibility of ensuring transparency, inclusivity, and accountability by deploying agents and observers on Election Day. the Coalition.

Dooroh borxih eglak fayseenit makaadoh adoytit samlissuh poropozaal seeco

Ityoppiyak Dooroh Egla (CEO) 190 daga takke adoytit le massoynaanih adoytit edde anuk Meqem kaban kee Doolat akke sinni Ayyuntiinoh Egla kinni. Egla sugte 

Ayyunti Ayyuntih Miraacinu (ACSO) Federal Ximokraatik Riboblik Ityoppiyak (FDRE) Sanat 2011 Ayyunti Eglah Maybalaalaqa Ixxima 1113/2019 Maysarraqa Ixxima 4748 Luk Amrisen. 

Ta Egla Itiyoppiyak Ayyuntih Eglaali Dooro Wagsiisiyyay, Ayyuntiino Kee Dooro Marih Barittooy, Dooro Booditteh Kalaluuy, Adoytiitih Dudda Dadlisoonuh Leh Yan Doori Aysaxaaxag Kee Koobaahisoonuh Xissimteh Tanim Tamixxige. 

Ta Alliance xissimteek xabba haanam 2011 Sidaama Rakaakayak Doolatak Margaqa, 2013 Amolladi Dooro (Juun 21, 2013 kee September 30, 2014), 2013 Gabbi Ayro Mawqah Itiyoppiyah Ummattah Rakaakayih Doolatak15 Margaqa, kee Sanat 2016 Benishangul Gumuz, Qafar, Fanti Itiyoppiya Kee Soomaalî Rakaakayittek Ossotinah Dooro Kee Qagaaqagitak Dooro. Ta Alliance Demokraasih Institutionitte Kee Baaxo Xayloh Gabat Agle Maqarosoonuh Baxaabaxsa Le Dacayri Kee Ayyuntiino Barittoh Taamoomi Gexisen. Tama Egla Yamaate 7hytoh Amolladi Dooroh Dooro Wagittaamal Mihratleelah Fayi Akah Yacen Innah Metteebanni Fayi Makaado Xisak Geytimta. Ta Fayi Makaado Ayfaf Tacelem Maytani Mihratleela Makaado Xayoosak Eglah Borxi Fayale Caddoh Metteebanni Fayu, Makeelo kee Qawwalaylah Kusaq Gitah, Qadliino sinnim kee Mihratiinole Dooroh Wagitto Yasmitoonuh. Ta Makaado Gana kee Kiniyal Geytimta Eglak Fiqma Dooro Lowsis Buttaati Abak Raag Akah Geytannah Gabbaaqu Sekkacsaanamay, Madqa Kee Amni Qawwalaylooli Fayisaanam Kee Dooro Tekkooka Makeelisak Eglak Dooro Lowsis Numma Akah Yasmiten Innah Abak Geytimaanam Warsen. 

Ta egla inkih tan rakaakay xaylo, sivil society massoynaani, barittô buxaaxi kee mihrat retteemah exxaaxi ta makaadoh addat geytimtah tan duddale maritte (sinni edde anuk) akah dooran innah arcibisa. Ta Ayyunti Seeco Itiyyobiyak Baxaabaxsale Baxaabaxsale Mihratleelaay, Numiino kee Awlaytiinoh Naharsino Yaceenim Baxaabaxsale kee Xaylol Rakuh tan Dooroh Gexsit Yasmiteenimi.

Fayi makaadoh gurummaca.

Ta Makaado leceey (6) takke. adoytit akkeleeh, ken fanak numuk tii ciggiltah tan luddittel mihratli akkele. 

1. Gaanun (doorô gaanun, doolát madqah gaanun, hinnay seehadayti baxi cakki) 

2. Siyaasâ misso ( Siyaasaay, bood kee doorô gexsitih makeelisso) 

3. loowo ( loowo, oyti makeelo) 

4. Oyti Teknolooji ( Xijitaal Amni, Dooroh Teknolooji, hinnay Oyti Siirat) 

5. Xaagi Qawaytu kee Angaaraw (Istraateejik Angaaraw) 

6. Amni Qawwalaylah kusaq ( bood makeelo hinnay amni miracsenta) 

Adoytiinu Faxxiimaama 

Fayxi le mari ciggiltah tan dagnal raqtam kibtam faxxinta: 

● Dagal galab kak xagneh nan luddittek tiyak teynal degree yaallem faxximta. 

● Dagnal koona (5) sanatih taamah abak raag loonum faxximta. 

● Demokraasih madqooqi, sittin way kee partitteh addat tan sittin way (siyaasâ partitte kee dooro gexsitit gabah agle sinni partitte luk angaaraw sinni) diggoysaanam. 

● maqar le adariinoh caddooda, weelo sinnim kee nummiino. 

Itiyoppiyal nado, xagar erkannaa kee kedooda wagittaamal baxsa le gurral tanbulle macal akkele. Adoytit 

namma sanatih waktih mekla sinnim labbatliinoh ayfaafay yacee.    Fayxi mannal doorimeleeh? 

faxita dooroonuh ( hinnay isih dooraanam), ciggiltah tan sanaditte faxximta: 

● sinni dooritte faxita marah, CV ken duddaay, abak raag kee celtah tan mayso taybulle. 

● Hadaf maybalaalaqa (1 gali) too ken uguugus baxxaaqissam, mihratiini mihrat kee demokraatak dooroh gexsititteh gulgulusso, 

gersi num doore koo tekkek,

faxita marih ux baxxaqsa; kalah ux maybalaalaqa edde anuk baxxaaqissam macaay atu elle taaminem atu raqtem kibtam. 

Assabalta rubtam faxximta galelastah info@cecoe.org ( hinnay ni weebsaayitil culmah cibta hinnay 

Garkureenit "Faysi makaadoh faxita" imeel ammuntih firtal yaybulleenim faxxinta. 

Assabalta oggoloonuh illacaboh ayro: caxah alsak 28, 2028. 

udurrutte assabalta oggol mali.

Doorô gexsit 

Inkih tan faxita mari qaddoysaanam kee xiqtol rakitteh tan agaarad gexele: 

1. Qimboh addah fokkaaqo Eglak Dooro Kutbeh Buxal, Daggowwa Lem Kibbimtuh. 

2. Mabla garay akkek maybalaalaqâ seeco edde anuk maybalaalaqah qunxa makaadoh sekkacsa. 

3. Illacaboh fayi eglak dooro borxih faaticissot xayyoowele. 

doorimte adoytit maarich alsak 31, 2026 aysixxigelon. 

Macaay gabat agle lem? 

Itiyoppiyal Demokraasi Gexsot Mihratleela Doorak Diggoysoonuh Cato Abeloonum Warsen. Fayi Makaado 7hytoh Amolladi Dooroh Numiino Diggoosoonuh Faximtah Tan Doori Digirele. 

kee inkih tan ityoppiyah xayloh tuxxiq leh tan waktil kee mihratiini wagitto yasmiteenimi. 

esseroora akkek ossotina xaagih, ni kutbeh buxat ongoorow info@cecoe.org Itiyoppiyak Ayyuntih Eglaali Dooroh Egla ( Dooroh Egla) 

Addis Ababa; Itiyoppiya 

Caxah alsak 2, 2018

Call for Nominations: Advisory Committee Members for CECOE’ Election Observation in the 7th General Election

The Coalition of Ethiopian Civil Society Organizations for Elections (CECOE) is a non-profit and non-governmental civil society organization comprising more than 190 member organizations. CECOE was licensed in 2019 by the Federal Democratic Republic of Ethiopia Authority for Civil Society Organizations (ACSO) under registration number 4748, in accordance with the Civil Society Organizations Proclamation No. 1113/2019. The organization was established to enhance and coordinate the role of Ethiopian civil society organizations in election observation, civic and voter education, prevention of electoral conflicts, and capacity building for its members.

Since its inception, CECOE has observed the 2019 Sidama Region Referendum, the 2021 General Elections (June 21 and September 30, 2021), the 2021 South West Ethiopia Peoples' Region Referendum, the 2023 South Ethiopia and Wolaita Zone Referendum rerun, and the 2024 outstanding and re-elections in parts of the Benishangul Gumuz, Afar, Central Ethiopia, and Somali regions. Additionally, CECOE has engaged in various advocacy and civic education activities and implemented projects to strengthen democratic institutions and citizen participation.

In line with this principle, CECOE is in the process of establishing a Technical Advisory Committee to provide expert guidance on election observation for the upcoming 7th General Election. This Advisory Committee will serve as a standing resource pool of experts, offering high-level technical advice, analysis, and risk assessment to support CECOE's Board in ensuring accurate, neutral, and impactful election observation. Drawing inspiration from international best practices, such as those from CODEO in Ghana and ELOG in Kenya, the Committee will enhance the credibility of CECOE’s observation efforts by reviewing reports, advising on legal and security risks, and analyzing electoral incidents.

CECOE invites all citizens, civil society organizations, academic institutions, and professional networks to nominate qualified individuals (including self-nominations) for membership on this committee. This public call aims to ensure a diverse, merit-based selection process that prioritizes expertise, integrity, and representation from across Ethiopia.

Composition of the Advisory Committee

The Committee will consist of six (6) members, with one expert selected from each of the following fields:

  1. Law (Electoral Law, Constitutional Law, or Human Rights)
  2. Political Science (Political Analysis)
  3. Statistics (statistician, Data Analysis )
  4. Information Technology (Digital Security, Election Technology, or Data Systems).
  5. Journalism and Communication (Strategic Communication).
  6. Security Risk Assessment (Conflict Analysis or Safety Protocols)

Criteria for Membership

Nominees must meet the following minimum requirements:

  • An academic degree in one of the specified fields.
  • At least five (5) years of working experience in their area of expertise. 
  • Demonstrated commitment to democratic principles, impartiality, and non-partisanship (no active affiliation with political parties, candidates, or government bodies involved in elections). 
  • Strong ethical standards, with a track record of neutrality and integrity. 

Diversity in gender, ethnicity, and regional representation will be prioritized to reflect Ethiopia's rich societal fabric. Members will serve voluntarily for a renewable two-year term without payment.

How to Nominate?

 

  • To self-nominate please submit the following documents: A Curriculum Vitae (CV) highlighting the nominee's qualifications, experience, relevant achievements and a Statement of Interest (1 page) explaining the nominee's motivation, how their expertise aligns with CECOE's mission, and their commitment to democratic election processes
  • If nominating someone else, include a brief note explaining why you believe they meet the above requirements, along with contact details so the CECOE secretariat can request the CV and statement of interest. 

Submissions should be sent via email to info@cecoe.org . Please indicate the specific field of expertise in the subject line "Nomination for Advisory Committee.”  

Deadline for Submissions

March 7 , 2026. Late submissions will not be considered.

Selection Process

All nominations will undergo a transparent, merit-based review: 

  1. Initial screening by the CECOE Secretariat to ensure the minimum criteria are met. 
  2. Evaluation by a vetting subcommittee, which may include interviews or reference checks.
  3. Final recommendations submitted to the CECOE Board for approval. 

Selected members will be notified by March 31, 2026. 

Why Participate?

By nominating experts, you help strengthen Ethiopia's democratic processes. The Advisory Committee will play a vital role in contributing to the integrity of the 7th General Election, ensuring timely and professional observation that benefits all Ethiopians. 

For inquiries or additional information, contact our Secretariat at info@cecoe.org

Coalition of Ethiopian Civil Society Organizations for Elections (CECOE)

February 9 2026 Addis Ababa, Ethiopia